YT_TheGeneration

                                                                            YaTewlidTheGeneration

የኢትዮጵያ የሰላምና የዴሞክራሲ አማራጭ ኃይሎች ምክር ቤት

በታህሳሥ 1986 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ የታቀደው የሰላምና የዕርቅ ጉባዔ ተካሂዷል። በጉባዔው ላይ በሀገር ቤትና ከሀገር ውጭ ያሉ፤ የታገዱና ያልታገዱ፤ ሁለ-ገብ ትግል የሚያካሂዱና በሰላም ብቻ የሚታገሉ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ የሙያ ማህበራት፤ የሲቪክ ማኅበረሰብ ተወካዮችና ታዋቂ ግለሰቦችም እንዲሁም የገዥው ፓርቲ ተወካዮች እንዲሳተፉ ጥሪ ተላልፏል።

ምንም እንኳን ሕወሀት/ኢሕአዴግ በዚህ ጉባዔ ላለመገኘት ቢወስንምና ለዚሁ ስብሰባ ከውጭ የመጡትን የድርጅቶች ተወካዮችን አስሮ (አቶ አበራ የማነ አብ ከመኢሶን፣ ወ/ሮ ገነት ግርማና አቶ መስፍን ተፈራ ከኢሕአፓ) ወዲያውኑ ወደ ወህኒ በመወርወርና የተለያዩ ተጽእኖዎች በማድረግ ስብሰባውንም ለማጨናገፍ ቢሞክርም፤ ጉባዔው እንደታቀደው ሊካሄድ ችሏል። ጉባዔው ሰፋ ያለ ቁጥር ያላቸውን የፖለቲካ ድርጅቶች ያቀፈ የአማራጭ ኃይሎች ምክር ቤትን መስርቷል።

ስለ የኢትዮጵያ የሰላምና የዴሞክራሲ አማራጭ ኃይሎች ም/ቤት  የተለያዩ ሠነዶች ያላችሁ ትልኩልን ዘንድ ትብብራችሁን እንጠይቃለን።

እትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

Long Live Ethiopia!

......ያ ትውልድ......
ታሪካችሁ ህያው ነው!

The Generation is Immortal!

 

እኛን ማግኘት/Contact us

This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

703 300 4302